Posts

Showing posts from November, 2010

ጥቂት ስለ ጾም

ምንጭ:-  ከማህበረ ቅዱሳን በማሞ አየነው                ሰው የነፍስና የሥጋ ውህድ ፍጡር ነው፡፡ በመሆኑም የነፍሱን ጥም በቃለ እግዚአብሔር ሲያረካ እንደ ሥጋዊነቱ ደግሞ ሥጋዊ ምግብን ይመገባል ይጠጣል፡፡ በነፍስና በሥጋ መካከል ያለው መሠረታዊ ልዩነት ነፍስ ኢመዋቲ ሥጋ ደግሞ መዋቲ መሆናቸው ነው፡፡ በሌላ ገለጻ ሥጋ ያለነፍስ ሕይወት የላትም፡፡ ነፍስ ያለሥጋ ብቻዋን ጽድቅን እንደማትፈጽም ሁሉ ያለምግበ ሥጋም ሥጋ ቀዋሚ አይደለችም፡፡ ስለዚህም ነው ጽድቅ የነፍስና የሥጋ ጥምር ድርጊት የሆነ ነው፡፡