Posts

Showing posts from July, 2010

ቅዱስ ጴጥሮስ እና ቅዱስ ጳውሎስ

Image
ዲያቆን ታደሰ ወርቁ እነዚህ ሁለት ቅዱሳን አባቶቻችን የቅድስት ቤተክርስቲያናችን አዕማድ ናቸው፡፡ በመሠረትነት በአጸኗት ቤተክርስቲያን ያላቸው የክብር ሥፍራ ላቅ ያለ ነው፡፡ ይህ የሆነው እንዲሁ አይደለም፡፡ ለቤተክርስቲያንና በቤተክርስቲያን የፈጸሙት አገልግሎት በዚህም የተቀበሉት ሰማዕትነት ነው፡፡ ቅዱሳት መጻሕፍትም ይህን መልካም የሆነውን ታሪካቸውን ለእኛ አርአያነት በሚሆን መልኩ ከትበውልናል፡፡ እኛም ለአርአርያነት በሚሆን መልኩ የእነዚህን ደጋግ ሁለት ቅዱሳን አባቶች ታሪክ፣ ዕውቀትና መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን ከዚህ በመቀጠል አቅርበናል፡፡ 1. ሁለቱ ሐዋርያት ሲጠሩ የነበሩበት ሕይወት ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በገሊላ ባሕር ዳር በምትገኘው በቤተ ሳይዳ ሲወለድ ሐዋርያው ቅዱስ ጳዉሎስ ደግሞ በጠርሴስ ከተማ ተወለደ፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ከወንድሙ ከእንድርያስ ጋር በገሊላ ባሕር ዓሣ ማሥገር ጀመረ፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳዉሎስ ደግሞ በ 15 ዓመት ዕድሜው በገማልያ ትምህርት ቤት በመግባት የአይሁድን ሕግና ሥርዓት ተምሯል፡፡ በ30 ዓመቱም የአይሁድ ሸንጎ አባል ሆኗል፡፡ /1ቆሮ.1.17፤ሐዋ.22.3/

«ሐነጸ መቅደሶ በአርያም፤ መቅደሱን በአርያም /በልዕልና/ አነጸ»

በዲ / ን በረከት አዝመራው ሰኔ 20 እና 21 በእመቤታችን ስም በፊልጵስዩስ የታነጸችው የቤተክርስቲያን መታሰቢያ በዓል ነው፡፡ ይህች ሃገር ቅዱስ ጳውሎስና ሲላስ ተዘዋውረው ያስተማሩባትና ብዙ ምዕመናንን ያፈሩባት ቦታ ናት፡፡ ከዚያም በኋላ በዚህች ቦታ የመጀመሪያዋ በእመቤታችን ስም የታነጸች ቤተ ክርስቲያን መተከሏን የሰኔ 20 ስንክሳርና ሌሎችም ምንጮች ይጠቁማሉ፡፡ የዚህ ጽሑፍ ዓላማ የሕንጻ ቤተ ክርስቲያንን ምሥጢራዊ /mystical/ መልዕክቶች ከብዙ በጥቂቱ ማብራራት ነው፡፡ እያንዳንዱ ምዕመን እንደ ጥረቱና እንደ መንፈሳዊ እይታው ብዙ ድንቅ መልዕክቶችን ቢያገኝም ከብዙ ጥቂቱ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያንና ማኅበረ ምዕመናን በግእዝና በአማርኛው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ « ቤተ ክርስቲያን » ተብሎ ተተርጉሞ የምናገኘው « አቅሌስያ » የሚለው የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙም « የኅሩያነ እግዚአብሔር ፣ የምዕምናን አንድነት » ማለት ነው፡፡ በኦርቶዶክሳዊት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይህ ስም ከማኅበረ ምዕመናን በተጨማሪ ለሕንፃ ቤተ ክርስቲያንም ይሰጣል፡፡ ይህም ሐዋርያዊ ትውፊት ነው፡፡ በሐዋርያት ዘመን ምዕምናን የሚገናኙበት ቤትም ፣ የምዕምናኑ አንድነትም « ቤተ ክርስቲያን » እየተባለ ይጠራ ነበር / ሮሜ 16.5 ፣ 1 ቆሮ . 11.8/ ፡፡ ዛሬም ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያናችን ይህን ትውፊት ጠብቃ ሕንፃውንም ማኅበረ ክርስቲያኑም « ቤተ ክርስቲያን » እያለች ትጠራለች፡፡ የቤተ ክርስቲያን ትምህርትና ሕይወት ረቂቅና ምጡቅ፣ በመንፈስ